ግንቦት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ የኢራን የጦር ኃይሎች በኩዌት እና በባህሬን የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማትን ኢላማ ያደረገ ሰፊ የሚሳይል እና የድሮን ጥቃት ሰንዝረዋል። በዚህ ጥቃት ሳቢያ በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ የአንድ ንጹህ ዜጋ ሕይወት ሲያልፍ፣ በደርዘን የሚቆጠሩ መቁሰላቸው ተረጋግጧል። ክስተቱን ተከትሎ ኩዌት እና ባህሬን የኢራንን ድርጊት በፅኑ አውግዘዋል።
የኩዌት መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳውድ አብዱልአዚዝ አል-ኦታይቢ በሰጡት መግለጫ፣ ረቡዕ ዕለት መንፈቅ ሌሊት ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው የጠላት ድሮኖች የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ተርሚናል 1 (Terminal 1) ንዑስ ክፍል መምታታቸውን ይፋ አድርገዋል። ጥቃቱ በአውሮፕላን ማረፊያው ሲቪል መሠረተ ልማት ላይ ከፍተኛ የቁስ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በወቅቱ በአካባቢው የነበሩ በርካታ ሰዎችን አቁስሏል።
የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ መሰረት በጥቃቱ የአንድ ህንዳዊ ዜጋ ሕይወት ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን፣ ከፍተኛ የጭንቅላት እና የፍንዳታ አደጋ የደረሰባቸውን ጨምሮ 63 ሰዎች የአደጋ ጊዜ ቀዶ ጥገና እና የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። አደጋውን ተከትሎ የንግድ በረራዎች በሙሉ ተቋርጠው የነበረ ቢሆንም፣ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ከሌሎች ተርሚናሎች በከፊል መጀመራቸው ተገልጿል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ምክር ቤት (IRGC) በበኩሉ ጥቃቱን በይፋ የሰነዘረ መሆኑን ባይክድም፣ ኢላማው የሲቪል አውሮፕላን ማረፊያ ሳይሆን በኩዌት የሚገኘው አሊ አል ሳሌም የአሜሪካ አየር ማዕከል (Ali Al Salem Air Base) እና በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ 5ኛ የባህር ኃይል እዝ መሆኑን አስታውቋል። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው ከሆነ፣ ይህ ጥቃት የተሰነዘረው አሜሪካ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ በምትገኘው የኢራኗ ቀሽም ደሴት (Qeshm Island) ላይ ላደረሰችው የድሮን መቆጣጠሪያ ጣቢያ ጥቃት እና በአንድ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ለፈጸመችው የሚሳይል ድብደባ የተሰጠ ቀጥተኛ የአጸፋ ምላሽ ነው። ኢራን አክላም የኩዌት እና የባህሬን መንግሥታት ግዛቶቻቸውን አሜሪካ በኢራን ላይ ወታደራዊ ጥቃት እንድትሰነዝርበት በመፍቀዳቸው ለተፈጠረው ጥፋት ቀጥተኛ ኃላፊነት አለባቸው ስትል ወንጅላለች።
በአካባቢው የሚገኘው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) በበኩሉ፣ ኢራን ወደ ኩዌት እና ባህሬን የላከቻቸውን ከ30 በላይ ባሊስቲክ ሚሳይሎች እና ባለአንድ አቅጣጫ ተወርዋሪ ድሮኖች (Kamikaze drones) የአሜሪካ እና የባህሬን የአየር መከላከያ ሥርዓቶች ማክሸፍ መቻላቸውን ገልጿል። ይሁን እንጂ የኩዌት ጦር ኃይሎች በሰጡት መረጃ፣ አንዳንድ የሚሳይል ስብርባሪዎች እና ድሮኖች በመኖሪያ መንደሮች እና በሲቪል ተቋማት ላይ ማረፋቸውን አረጋግጠዋል።
ይህ የቅርብ ጊዜ እርስ በርስ የመጠቃቃት እርምጃ፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ባለፈው ሚያዝያ ወር ተደርሶ የነበረውን ተሰባሪ የተኩስ አቁም ስምምነት ለአደጋ ያጋለጠ ሲሆን፣ በፋርስ ባህረ ሰላጤው የነዳጅ ማጓጓዣ መስመር ላይ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ስጋት ፈጥሯል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ከአንጋፋዋ የኪነጥበብ ሰው #አለምጽሃይ ወዳጆ ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/NybH5JhdaNs
read more
ትራምፕ ለታይዋን የሚሰጠውን 400 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ አገዱ
መስከረም 09 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ጋር የንግድ ስምምነት ለማድረግ እና የመሪዎች ስብሰባ ለማዘጋጀት እየሞከሩ በመሆናቸው ለታይዋን የሚሰጠውን... read more
በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንቶሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ
ታኅሳስ 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንቶሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል... read more
ህፃን አግተው ገንዘብ የጠየቁ ግለሰቦች በጽኑ እስራት ተቀጡ
ግንቦት 05 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የ6 ዓመት ህፃን በማገት እና ቤተሰቦቹን ለገንዘብ በመደራደር ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች በ12 እና በ9... read more
የተፈጥሮ ጥርስን እንደገና ማብቀል የሚችል መድኃኒት በሰው ላይ መሞከር ተጀመረ
ጥቅምት 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ጃፓን ሰው ሰራሽ ጥርሶችን (Dentures) እና የጥርስ ተከላዎችን (Implants) ወደ ታሪክ የሚሰድ አዲስ ዘመን ሊከፍት... read more
ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ በሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ላይ የ14 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ
ፍርድ ቤቱ ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የ14 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል፡፡
ፖሊስ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት... read more
የትግራይ ክልል የኩላሊት ሕመምተኞች በገንዘብ እጥረት እና በአካባቢው ባለው ውጥረት ምክንያት ከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ
ሕዳር 10 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በገንዘብ እጥረት እና በአካባቢው ባለው ውጥረት ምክንያት የትግራይ ክልል የኩላሊት ሕመምተኞች ከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸውን... read more
በአፍርካም ሆነ እንደ ኢትዮጵያ ስደትን ለመቀነስ እና ተመላሾችን ለማቋቋም ጠንካራ የፋይናስ አማራጭ መዘርጋት እንደሚገባ ተጠቆመ
ስደትን ለማስቆምና ከስደት ተመላሾችን ለማቋቋም አጋዥ አካላት እንደሚያስፈልጉ የካርቱም ፕሮሰስ በተሰኘ በስደትና ከስደት ተመላሾች ዙሪያ የሚሰራ ተቋም ባዘጋጀዉ መድረክ ላይ... read more
የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሀገሪቱ በተለያዩ የከተማ መግቢያና መውጫ ላይ ለኮቴ የሚከፈለው ክፍያ ከተቋሙ እዉቅና ዉጪ ህጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ተግባር ነዉ አለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሕዝብና የጭነት አጓጓዞች በሆኑ ተሽከርካሪዎች በየከተማው የሚሰበሰቡ የኮቴ ክፍያዎች ሕጋዊነት የሌላቸዉ መሆኑንና የብዝበዛ ድርጊት እየተፈፀመ... read more
ተማሪዎች ለሱስ ተጋለጭ እንዳይሆኑ ወላጆች ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ተባለ
መስከረም 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም ሁሉም ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ስራ መጀመራቸው ይታወቃል። ከዚህ ጋር... read more
ምላሽ ይስጡ