ግንቦት 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ መተላለፍ ምክንያት የመራጮች ምዝገባ በታገደባቸው አካባቢዎች፣ በድምፅ መስጫው ዕለት የመራጮች ምዝገባ ተካሂዶ ሕዝቡ በምርጫው እንዲሳተፍ እንደሚደረግ አስታወቀ። ቦርዱ በተጨማሪም ለቅሬታና ጥቆማ ማቅረቢያ የሚሆን ነፃ የስልክ መስመር ማዘጋጀቱን ገልጿል።
የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ቦርዱ በድህረ-ምርጫ ወቅት ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፣ ከቦርዱ ሕግ ውጪ የመራጮች ምዝገባ ሲያከናውኑ የነበሩ በርካታ ምርጫ ጣቢያዎች በክትትልና በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት በጊዜያዊነት እንዲታገዱ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች የመምረጥ መብታቸው እንዳይጣስ ለማድረግ ልዩ ዝግጅት መደረጉን ዋና ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው የድምፅ መስጫ ዕለት፣ በእነዚሁ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በአንድ ላይ ተከናውኖ ሕዝቡ ቀጥታ በምርጫው እንዲሳተፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለቅሬታ ማቅረቢያ “6214” የነፃ ስልክ መስመር ተዘጋጅቷል
ምርጫ ቦርድ የምርጫው ሂደት ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን ለማገዝ፣ በምርጫው ዕለት ለሚያጋጥሙ ማንኛቸውም ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ማስተናገጃ የሚሆን 6214 የተሰኘ ነፃ የጥሪ መስመር ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
ቦርዱ ለሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ሙሉ ዝግጁነት እንዳለው ያስታወቀ ሲሆን፣ ዜጎች በምርጫው ሂደት ላይ የሚታዘቧቸውን ሕገ-ወጥ ድርጊቶችና ቅሬታዎች ይህንን የነፃ ስልክ መስመር በመጠቀም እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የቢሊየነሩ የፅሁፍ ስህተት ውዝግብ አስነሳ፤ የኢራን ቆንስላ ለኢሎን ማስክ “ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልግሃል!” ሲል መለሰለት
ሰኔ 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኤክስ (X) ባለቤትና ታዋቂው ቢሊየነር ኢሎን ማስክ በስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ስያሜ ዙሪያ በገጹ ላይ ያሰፈረው... read more
ኢንዶኔዥያ በዶናልድ ትራምፕ አዲስ የንግድ ስምምነት መሰረት 19 በመቶ ቀረጥ ትከፍላለች
👉50 ቦይንግ አውሮፕላኖችንም ትገዛለች ተብሏል
ሐምሌ 09 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ኢንዶኔዥያ ወደ አሜሪካ ለሚገቡ ምርቶቿ የምትከፍለው ቀረጥ... read more
በኒው ዮርክ የመጀመሪያው ሙሉ የሰው ዓይን ንቅለ ተከላ ተደረገ፤ ወደ ዕይታ ተስፋ የሚያመራ እርምጃ ነው ተብሏል
ሕዳር 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በሕክምና ሳይንስ ታሪክ ውስጥ እጅግ ትልቅ ምዕራፍ ተብሎ የተመዘገበ ታሪካዊ ክስተት በኒው ዮርክ ላንጎን ጤና ተቋም... read more
ለሙት አንሳ ገዳም የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ 30 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገለጸ
መስከረም 14 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር፣ ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው የሙት አንሳ ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መነኮሳትን... read more
“ምንም ሳላጠፋ ነው የተቀጣሁት” ሲል አነጋጋሪው ተጫዋች ፕሬስቲያኒ በአዲስ ቃለ መጠይቅ ተናገረ
መጋቢት 25 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ጂያንሉካ ፕሬስቲያኒ በቪኒሲየስ ጁኒየር ላይ የዘረኝነት ስድብ ሰድቧል በሚል የቀረበበትን ክስ በአዲስ ቃለ መጠይቅ ያስተባበለ ሲሆን፤... read more
የአድዋ ድልን በስነ-ስዕል በመግለጽ ረገድ ገና እንዳልተሰራበት የዘርፉ ባለሙያዎች ገለጹ
የካቲት 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ታሪክን በሙዚቃ፣ በስዕል፣ በተውኔት እና በሌሎች ኪነጥበባዊ ስራዎች የመግለጽ እድል ቢኖርም ኢትዮጵያ ታሪካዊ ሁነቶቿን በተገቢው መልኩ... read more
በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው የሠላም ንግግር በሌሎች አካባቢዎችም ሊስፋፋ ይገባል ተባለ
ኅዳር 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል የተጀመሩ የሠላም ንግግሮች በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም ተግባራዊ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ የስነ አመራር መምህር... read more
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀን 11/02/2017 ዓ/ም በጻፈው ደብዳቤ 11 ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዳገዳቸው ይታወቃል፡፡
ከእነዚህም ውስጥ 5ቱ ፓርቲዎች /የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፤ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፤ የጋምቤላ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ፤ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት እና አገው ለፍትህ... read more
የአሜሪካ የኑክሌር ሚስጥር በዲጂታል ካርዶች አማካኝነት ለዓለም ተጋለጠ!
ሚያዚያ 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ባለፈው የፈረንጆች አመት ቤሊንግካት (Bellingcat) የተባለው የምርመራ ተቋም ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሜሪካ አየር ሃይል አባላት... read more
ለሁለት ዓመታት ብቻውን በአፓርታማ ውስጥ የተረሳው የ9 ዓመቱ ታዳጊ
ታህሳስ 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በፈረንሳይ አንድ የ9 ዓመት ታዳጊ ህጻን ለሁለት ዓመታት ያህል ያለምንም ተንከባካቢ በአፓርታማ ውስጥ ብቻውን መኖሩ ተሰማ።... read more
ምላሽ ይስጡ