ግንቦት 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ መተላለፍ ምክንያት የመራጮች ምዝገባ በታገደባቸው አካባቢዎች፣ በድምፅ መስጫው ዕለት የመራጮች ምዝገባ ተካሂዶ ሕዝቡ በምርጫው እንዲሳተፍ እንደሚደረግ አስታወቀ። ቦርዱ በተጨማሪም ለቅሬታና ጥቆማ ማቅረቢያ የሚሆን ነፃ የስልክ መስመር ማዘጋጀቱን ገልጿል።
የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ቦርዱ በድህረ-ምርጫ ወቅት ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፣ ከቦርዱ ሕግ ውጪ የመራጮች ምዝገባ ሲያከናውኑ የነበሩ በርካታ ምርጫ ጣቢያዎች በክትትልና በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት በጊዜያዊነት እንዲታገዱ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች የመምረጥ መብታቸው እንዳይጣስ ለማድረግ ልዩ ዝግጅት መደረጉን ዋና ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው የድምፅ መስጫ ዕለት፣ በእነዚሁ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በአንድ ላይ ተከናውኖ ሕዝቡ ቀጥታ በምርጫው እንዲሳተፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለቅሬታ ማቅረቢያ “6214” የነፃ ስልክ መስመር ተዘጋጅቷል
ምርጫ ቦርድ የምርጫው ሂደት ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን ለማገዝ፣ በምርጫው ዕለት ለሚያጋጥሙ ማንኛቸውም ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ማስተናገጃ የሚሆን 6214 የተሰኘ ነፃ የጥሪ መስመር ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
ቦርዱ ለሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ሙሉ ዝግጁነት እንዳለው ያስታወቀ ሲሆን፣ ዜጎች በምርጫው ሂደት ላይ የሚታዘቧቸውን ሕገ-ወጥ ድርጊቶችና ቅሬታዎች ይህንን የነፃ ስልክ መስመር በመጠቀም እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በጀርመን እስረኛ ከእስር ለማምለጥ ቢሞክር ወንጀል አይደለም ተባለ
👉ነጻነትን የማግኘት ሙከራ ሰብዓዊ መብት ነው ተብሏል
ሐምሌ 29 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የጀርመን የፍትህ ስርዓት በአንድ አስገራሚና ልዩ ህግ ይታወቃል የተባለ ሲሆን... read more
በኢትዮጵያ ቋሚ የህፃናት የኩላሊት ዲያሊሲስ ህክምና መስጫ ተቋም አለመኖሩ ተገለጸ
በሃገሪቱ በኩላሊት በሽታ የተጠቁ ህፃናት ዲያሊስስ የሚያደርጉበት የህክምና መስጫ ተቋም አለመኖሩን በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ህክምና የኩላሊት ስፔሻሊስ ዶክተር... read more
በከባድ የሙስና ወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው አሥራ አንድ ተጠርጣሪዎች ክስ ተመስርቶባቸዋል – የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ
ሕዳር 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በከባድ የሙስና ወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው አሥራ አንድ ተጠርጣሪዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ክስ የተመሰረተባቸውም1ኛ ተከሳሽ... read more
የውጭ ባንኮች በሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቅድ አዋጅ ጸደቀ
ታኅሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የውጭ ባንኮች በሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሰሩ... read more
አዲስ የምርመራ ውጤት ሰውን ልዩ የሚያደርገው የዲ ኤን ኤ ክፍል በአንጎል እድገት ላይ ያለውን ሚና አሳይቷል
በዱክ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ማእከል የተመራ አዲስ ጥናት ሰዎችን ከሌሎች ዝርያዎች የሚለይ እና በአንጎል እድገት ላይ ወሳኝ ሚና የሚጫወት የዲ ኤን... read more
የፑቲን መልዕክተኛ የዩክሬን ጦርነትን በዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ ለመቋጨት ተቃርበዋል አሉ
ጥቅምት 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ልዩ መልዕክተኛ እንደተናገሩት፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ እና ዩክሬን አብረው በመስራት በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን... read more
ከዛሬ ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 6/2017 ዓ.ም ከ692ሺ በላይ ለሚሆኑ ሕጻናት የፖሊዮ ክትባት እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 03 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ለአራት ቀናት የሚቆይ የሁለተኛው ዙር የልጅነት ልምሻ /ፖሊዮ/ ክትባት ዘመቻ መጀመሩ... read more
የጥምቀት ኤክስፖ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊካሄድ ነው ተባለ
ታኅሳስ 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በመዲናችን አዲስ አበባ የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ የሚካሄደው ኤክስፖው ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ፤ ከሙዚቃ እና ከአልኮል... read more
በልምድ የሚሰሩ ዜጎችን የስራ ላይ ስልጠና በመስጠት ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ
በተለያዩ ተቋማት እንዲሁም በተለያየ መስክ ላይ የሚገኙና በልምድ የሚሰሩ ዜጎች ያላቸው ምርታማነት አንሳ በመሆኑ በተለያዩ ዘርፎች የሚፈለገውን ያህል ውጤት አለመገኘቱን... read more
ድሮኖቹ ቁጥጥር ከማድረግ በተጨማሪ #እርምጃም መውሰድ ይችላሉ ተባለ
👉የከተማዋን የፀጥታ ሁኔታና የትራፊክ ፍሰት ለመቆጣጠር ይሰማራሉ የተባሉ ድሮኖች ቁጥጥር ብቻ ሳይሆን እርምጃም እንደሚወስዱ ተገለጸ
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የትራፊክ ፍሰት... read more
ምላሽ ይስጡ