ግንቦት 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ መተላለፍ ምክንያት የመራጮች ምዝገባ በታገደባቸው አካባቢዎች፣ በድምፅ መስጫው ዕለት የመራጮች ምዝገባ ተካሂዶ ሕዝቡ በምርጫው እንዲሳተፍ እንደሚደረግ አስታወቀ። ቦርዱ በተጨማሪም ለቅሬታና ጥቆማ ማቅረቢያ የሚሆን ነፃ የስልክ መስመር ማዘጋጀቱን ገልጿል።
የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ቦርዱ በድህረ-ምርጫ ወቅት ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፣ ከቦርዱ ሕግ ውጪ የመራጮች ምዝገባ ሲያከናውኑ የነበሩ በርካታ ምርጫ ጣቢያዎች በክትትልና በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት በጊዜያዊነት እንዲታገዱ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች የመምረጥ መብታቸው እንዳይጣስ ለማድረግ ልዩ ዝግጅት መደረጉን ዋና ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው የድምፅ መስጫ ዕለት፣ በእነዚሁ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በአንድ ላይ ተከናውኖ ሕዝቡ ቀጥታ በምርጫው እንዲሳተፍ ይደረጋል ብለዋል።
ለቅሬታ ማቅረቢያ “6214” የነፃ ስልክ መስመር ተዘጋጅቷል
ምርጫ ቦርድ የምርጫው ሂደት ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን ለማገዝ፣ በምርጫው ዕለት ለሚያጋጥሙ ማንኛቸውም ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ማስተናገጃ የሚሆን 6214 የተሰኘ ነፃ የጥሪ መስመር ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
ቦርዱ ለሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ሙሉ ዝግጁነት እንዳለው ያስታወቀ ሲሆን፣ ዜጎች በምርጫው ሂደት ላይ የሚታዘቧቸውን ሕገ-ወጥ ድርጊቶችና ቅሬታዎች ይህንን የነፃ ስልክ መስመር በመጠቀም እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በአዋሽ ፈንታሌ እየወጣ ያለው የጋዝ መጠን እየጨመረ መሆኑን ተከትሎ ለአደጋ ተጋላጭ ናቸው የተባሉ 60ሺሕ ዜጎች በክልሉ በሚገኙ የአይ.ሲ.ቲ ፖርኮች እንዲሰፍሩ እየተደረገ ነው ተባለ
በአፋር ክልል ፈንታሌ ባልተለመደ መልኩ እየወጣ ያለው ሚቴን ጋዝ ከእሳተ ጎመራ ጋር ሊያያዝ ብሎም በአከባቢው የአየር ፀባይ ላይ ለውጥ ሊያመጣ... read more
ሳውዲ አረቢያ የእስራኤል በሶሪያ ላይ ያደረገችውን ወረራ አወገዘች
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በሶሪያ ግዛት ውስጥ በቅርቡ ያደረገችውን ወረራ በጽኑ አውግዟል። ሚኒስቴሩ... read more
ብቁ ያልሆኑ ዜጎች ለውጭ ሀገር የስራ ስምሪት እየተላኩ በመሆኑ ለስቃይ እየተዳረጉ ነው ተባለ
በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ብቁ ያልሆኑ ዜጎች እየተላኩ በመሆኑ ለስቃይ መዳረጋቸውን የፌደራል የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ጥናት ገለጸ።
ይህንን በተመለከተ የወጣው... read more
በአንድ “እምቢታ” የጣሊያንን ሕግ የቀየረችው የ17 ዓመት ወጣት ድፍረት!
👉ክብርን ለመጠበቅ ደፋሪን ማግባት ግዴታ ነው የተባለችው ፍራንካ ቪዮላ ማን ናት?
ጥቅምት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዛሬ ዓመታት በፊት በጣልያን ሲሲሊ ክልል... read more
በከተማዋ 19 መስመሮች እስከ ምሽት 4 ሰዓት በቋሚነት የአውቶቢስ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 21 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ የአውቶቢስ ትራንስፖርት አገልግሎት ከሚሰጡ መስመሮች 19ኙ በቋሚነት እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት አገልግሎት... read more
በመዲናዋ 340 የሚጠጉ የተለያዩ ኩነቶች ያለ ምንም የፀጥታ ችግር መከናወን ችለዋል ተባለ
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህንን ያለው የአዲስ አበባ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከተለያዩ አካላት ጋር እየመከረበት ባለበት መድረክ ላይ... read more
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተሰሩ ስራዎች ወደሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ በመተካት ከ2.8 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
ጥር 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በተለያዩ ዘርፎች ላይ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ከውጪ በሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች በመሸፈናቸው ከዚህ... read more
በሱዳን ዳርፉር ክልል በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ1,000 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ
ነሐሴ 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሱዳን ምዕራባዊ ዳርፉር ክልል ውስጥ በመራ ተራሮች አካባቢ ታራሲን በተባለች መንደር ላይ በደረሰ ከባድ የመሬት... read more
ሞሮኮ ከአለም ዋንጫ ዝግጅት ጋር በተያያዘ በርካታ ውሾችን እየገደለች እንደምትገኝ ተገልጿል
ሕዳር 04 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) ሞሮኮ ለዓለም ዋንጫ ዝግጅት በሺዎች የሚቆጠሩ ውሾችን በመንገድ ላይ በመግደል መከሰሷም ተሰምቷል።
የ2030 የዓለም ዋንጫን... read more
ምላሽ ይስጡ