የኢትዮጵያ ሚዲያ ዳሰሳ፡ በነፃነት፣ በኢኮኖሚ እና በፀጥታ ተግዳሮቶች መካከል
ሙሉ ዘገባውን ለመስማት ሊንኩን ይጫኑ
በተጠናቀቀው የበጀት አመት መገናኛ ብዙሃን መረጃ ለህዝቡ በተለያዩ አማራጮች ከማሻገር ባለፈ የነበራቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ሚና በተለያየ ሁኔታ ይነሳል ። በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በርካታ የሚድያ አማራጮች እየተስፋፉ መሆኑን ተከትሎ በተለይ ፈጣንና የተጣራ ትክክለኛ መረጃን ለህዝቡ ከማድረስ አንጻር የሚነሱ ክፍተቶች በርካታ ናቸው ።
በአጠቃላይ በአመቱ በዘርፉ የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን እንዲሁም በቀጣይ የሚድያው ዘርፍ በሃገራችን የሰላም፣የዲፕሎማሲ፣የፖለቲካና ቁልፍ ሃገራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የሚረው ተሳትፎ በምን መልኩ መሻሻል የኖርበታል የሚለው የዳሰሳችን መነሻ ሃሳብ ነው ።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚድያና ኮሙኒኬሽን መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አብዲሳ ዘራይ ፤ ባሳለፍነው 2017 ዓም አጠቃላይ በሚድያው ላይ የነበረው እንቅስቃሴ ፈታኝ እንደነበር ይገልጻሉ ። በተለይም ከሚድያ ነጻነት አንጻር በሃገሪቷ ባለው የሰላምና ጸጥታ ስጋት ግልጽ በሆነና ባልሆነ መልኩ ሚድያው በነጻነት ከመዘገብ የታቀበበት አመት ነበር ብለዋል።በተለይም ግጭቶች የነበሩባቸው ቦታዎች ላይ በነጻነት ተንቀሳቅሶ ያሉ ሁኔታዎችን ከመዘገብ አንጻር ምቹ ሁኔታዎች የጠበቡበት አመት መሆኑን አስታውሰው፤
የግል መገናኛ ብዙሃን በተለያየ ተጽኖ ስር የወደቀበት አመት በመሆኑ ሙያው በሚፈቅደው ልክ ያልተሰራበት ብሎም ዜጎች ማግኘት የሚገባቸውን መረጃ ማግኘት ያልቻሉበት አመት ነበር ሲሉ የሚገልጹት ዶ/ር አብዲሳ ፣ ሃገራችን ባለችበት የፖለቲካ ቀውስ ምክንያት ጋዜጠኞች ዘርፉን የመልቀቅ፣ ተሰዶ ወደውጪ ሃገራት የመሄድና ፤ በግሉ የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ የተሰማሩት በኢኮኖሚው ረገድ በደረሰባቸው ጉዳት እስከ መዘጋትና ከዘርፉ የመውጣት ሁኔታ ላይ የደረሱት በርካታ መሆናቸውን አብራርተዋል ።
ዘርፉ ላይ የተሰማራው ባለሙያ በራሱ ሞያው በሚፈቅደውና በተማረው የሙያ ዲሲፕሊን ልክ እንዳይሰራ ሚድያው ያለበት ተጽኖ ተግዳሮት በመሆኑ ነው የሚሉት ተመራማሪው ፤ ባለሙያው አሁን ላይ በዘርፉ እየሰራ ያለው ተጠያቂነትን የማያመጡ ጉዳዮችን ብቻ ነውም ብለዋል ። በተጨማሪም በመንግስት በኩል ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ደካማ መሆን ለግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ መዳከም ምክኒያት ነው ሲሉ አመላክተዋል ።
ባሳለፍነው 2017 ዓም በነበረው የስራ ዘመን መገናኛ ብዙሃን ፈታኝ የሚባሉ ጊዜያቶች እንደነበሩት ለጣቢያችን የገለጹት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያና በትርታ ኤፍ ኤም ከፍተኛ አዘጋጁ አቶ ዮሴፍ ዳሪዮስ ናቸው ። በነበሩ ሃገራዊ ችግሮች የፕሪንት መገናኛ ብዙሃኑ በርካታ ተግዳሮቶችን ያሳለፈበር ነበር የሚሉት ጋዜጠኛው ፤ ካሁን ቀደም የነበሩ ጋዜጣዎች በቁጥር መቀነስና በርካቶች ከዘርፉ የወጡበት እንደነበር ይገልጻሉ ። የመረጃ ምንጭ የሆኑ ተቋማት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ተፈላጊውን መረጃ በቀላሉ ማግኘት አለመቻል አንዱ በአመቱ ወስጥ ያጋጥም የነበረ ተግዳሮት እንደነበር ገልጸው ፤ እንዲህ አይነት ክፍተቶች ሚዛናዊ የሆነ ስራ እንዳይሰራ እንደሚያደርግና በቀጣይ ሊሻሻል የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል ። በሌላ በኩል የማህበራዊ ሚድያውን በመጠቀም ሙያውን በሚገባ የማያውቁና በዘፈቀደ መረጃን በቀላሉ ወደ ማህበረሰቡ የማሰራጨ ትሁኔታ ዘርፉንም ባለሙያውንም ወደውሃላ የጎተተ እንደነበር አመላክተዋል ።
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያው አቶ ዮናስ ወልደየስ የመገናኛ ብዙሃኑ በአጠቃላይ በአዋጅ በትደነገገለት መብት መሰረት ትከከለኛ መረጃን ለህዝቡ የማድረስና ሃሳብን ሚዛናዊ በሆነ መልኩ በነጻነት ተደራሽ የማድረግ ሙሉ መብት እንዳለው እንደሚደነግግ ብሎም የተቀመጠላቸውን ህግና ደንብ አክብረው ለሃገር አንድነት ሊሰሩ እንደሚገባ ህገመንግስታዊ ጥበቃም ያለው መሆኑን አስታውሰው ፤ በህጉ መሰረት ተጠያቂ እንደሚሆንም አብራርተዋል ።
መገናኛ ብዙሃኑ ለሃገር ከፍተኛ አስተዋጸኦ ያለው መሆኑን ተከትሎ ፤እንደ ሃሰተኛ መረጃ ማሰራጨት ያሉ በስራ ሂደት የሚፈጠሩ የህግ ጥሰቶችን በህግ መጠየቅ የሚያስቸል ድንጋጌ በመኖሩ ከጋዜጠኛ እስር ባለፈ ጣቢያውን እስከማሸግ የደረሰ እርምጃ እንደሚወሰድ ይደነግጋል ይላሉ ።
የአሃዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስኪያጁ ጋዜጠኛ ጠበቡ በለጠ ፤ ከጋዜጠኝነት ሙያ ጋር በተያያዘ በ አፍሪካ ልቀት ማዕከል ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ጋር ውይይት የተካሄደባቸው መድረኮች በ2017 ዓም የነበሩበት አመት እንደነበር አስታውሰው ፤ ባለፈው አመት እንደ ጋዜጠኛ አብዱል ሰመድ መሃመድና ዮናስ አማረ ያሉ ታዋቂ ጋዜጠኞች ድንገተኛ መሰወርና እስር የነበረበት አመት ነበር ብለዋል ።
ይሄም በሌሎች አለም አቀፍ ሚድያዎች አማካኝነት ሸፋን የተሰጠው በመሆኑ ለሃገራችን የመገናኛ ብዙሃን ገጽታ በአለም አቀፍ መድረክ ጥሩ እንዳልነበር ጠቅሰው በስፋት ሊሰራበትና ሊታይ የሚገባው ነው ብለዋል ።
በተለይም የንግድ መገናኛ ብዙሃን በመንግስት በኩል የሚደገፉ አለመሆናቸውን ጠቅሰው ፤ በአንድ አንድ ሃገሮች ካለው ልምድ በመነሳት ለሚድያዎች ቦታ በመስጠት የሚድያ መንደር የማቋቋም ስራዎች መሰራት እንደሚገባቸው ብሎም ለጎብኚዎች ክፍት በማድረግ ገቢ የሚገኝበትን ሁኔታ መፍጠር ይገባል ብለዋል ።
እንደቢራ ያሉ ስፖንሰሮችን ከሚድያው ዘርፍ ሙሉ ሙሉ በሙሉ ለማገድ በተሰራው ስራ የንግድ መገናኛ ብዙሃኑ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት እንዳደረሰባቸው ገልጸው ፤ የቢራ ማስታወቂያ በተዘዋዋሪ መንገድ በሌሎች እንደ ዴኤስ ቲቪ ባሉ አማራጮች በሌላ ሃገር በኩል የሚተላለፍ በመሆኑ እንደሃገር ሊገኝ የሚችለውን ገቢ እያሳጣ ነው ይላሉ።
ማስታወቂያዎችን ሙሉ በሙሉ ከማገዱ የልቅ ከሌሎች የአለም ሃገራት ልምድ በመውሰድ አማራጭ የመፍትሄ መንገዶችን በመጠቀም ከምሽት 3 ሰአት በውሃላ የሚተላለፉበትን አማራጭ መፍጠር ይገባል ብለዋል ።
የሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ታምሩ ጽጌ ፤ በተጠናቀቀው 2017 በህትመት ዘርፉ የህትመትና የወረቀት ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረበት አመት መሆኑን ተከትሎ አመቱ ከባድ እንደነበር አስታውሰዋል ። ከፍተኛ የሆነ ቁጥጥር የነበረበትና በርካታ ጋዜጠኞች የታሰሩበት አመት ከመሆኑ ባለፈ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ስበሰባዎች ላይ እንዳንገኝ የተደረግንበት አመት ነበር የሚሉት አዘጋጁ ፤
በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር በሞከርነው ኪደት አጥጋቢ መላሽ ያላገኘንበትም ነበር ይላሉ ። የሚፈጠሩ ከፍተቶችን በህግ አግባብ ከመጠየቅ ይልቅ መረጃ የመከልከልና ባለሙያዎችን የማሰር አሰራር እንደነበር አስታውሰው ፤ በዘንድሮው አመት ተጠባቂ ሃገራዊ መርጫም መኖሩን ተከትሎ መንግስትም ትኩረት አድርጎ ሊሰራበት እንደሚገባና ዘርፉን የማበረታታት ስራ ሊሰራ እንደሚገባ አመላክተዋል ።
የኢትዮጲያ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው ጋዜጠኛ መርሻ ጥሩነህ፤በ2017 ዓም በዘርፉ ላይ እንደ ማህበር ከተሰሩ ዋናዋና ስራዎች መሃል፤ ሚድያዎች በነጻነት እንዳይሰሩ እያደረገ ያለውን አዋጅ መልሶ እንዲሻሻል ለማድረግ እንደማህበር በርካታ ጥረቶች የተደረገበት አመት እንደነበር ገልጸው ፤ የማህበራዊ ሚድያዎች መስፋፋት በዘርፉ ላይ ያስከተለው ጫና ከፍተኛ እንደነበር ተናግረዋል ።
እንደማህበር ለጋዜጠኞች መብት መከበር የሚያግዙ ሃሳቦችን የመሰንዘርና የመሟገት ሰራዎች መሰራታቸውን የሚገልጹት ሃላፊው ፤ በተለይም ከጋዜጠኞች አፈና ጋር በተያያዘ ያሉ ከህግ አግባብ ውጪ የሆኑ ስራዎችን በመቃወም የመሟገት ስራዎች ተሰርተዋልም ነው የሚሉት ። ሚድያው ከፖለቲካ በጸዳ መልኩ ሰራውን እንዲሰራ ከማድረግ ና ዘርፉን ከማበረታታት አንጻር በመንግስት በኩል ሰፊ ክፍተት የነበረበት አመት እንደነበር አመላክተዋል ።
በኢትዮጲያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የማስታወቂያና የሚድያ ከትትል መሪ ስራ አስፈጻሚ ባለስልጣን ወ/ሮ የሺ ወርቅ ግርማ ፤ በተጠናቀቀው የ 2017 ዓም የስራ ዘመን ባለስልጣኑ በአዋጅ በተሰጠው ሰልጣን መሰረት በሃገር አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀስ በህትመት ፣በሬዲዮ ፣ ናቴሌቪዥንና በበይነ መረብ የሚንቀሳሰሱ የይዘት አመንጪዎችን በመመዝገብ ሃላፊነቱን የተወጣበት አመት እንደነበር ገልጸው፤ ሃገሪቱ ላይ የነበሩ በርካታ ሁነቶች ላይ ለመሳተፍ ይመጡ የነበሩ የውጪ ሚድያዎችም ተሳታፊ እንዲሆኑ በርካታ ፈቃዶች የተሰጠበት አመት እንደነበር ተናግረዋል ።
በሌላ በኩል በሃገር ወስጥ ያሉ መገናኛ በዙሃንን በወጡ መመሪያና ደንቦች እንዲሁም ሃገሪቱ ካስቀመጠቻቸው መተዳደሪያ ህግና ደንቦች አንጻር ክትትል፤ቁጥጥርና ድጋፎች የተደረገበት አመት እንደነበር አስታውሰው ፤ የሚድያ ባለሙያዎችን ፤ ባለበቶችንና ማህበረሰቡን በተለያየ ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል ።
በሚድያዎች ላይ የሚታየውን የአቅም ማነስና የባለሙያዎች ክፍተትን ከመፍታት አንጻር በርካታ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ባለስልጣኑ ተመልክቶ በቅድ መያዙን ተናግረዋል ። እንደምስራቅ አፍሪካም የመገናኛ በዙሃን የልቀት ማእከል ለመገንባት የመነሻ ሰራዎች መጀመራቸውንና በቀጣይ በሰፋት እንደሚሰራበት ገልጸዋል ።
የንግድ መገናኛ ብዙሃን አትራፊ ሆነው በተደራጀ አቅም እንዲቀጥሉና ዘርፉን ምቹ ከማድረግ አንጻር ባለስልጣኑ ድጋፍ ከማድረግ አንስቶ መተለያዩ የመንግስታዊ በሆኑና ባልሆኑ ተቁዋማት ተገኝተው መረጃ የሚያገኙበትን መንገድ በመፍጠር ብሎም የተለያዩ የመሳሪያ ድጋፎችን እንዲያገኙ እየሰራ መሆኑን የሚገልጹት ስራ አስፈጻሚዋ፤ የይዘት ጥራትና ተደራሽነት ላይ የተሻለ ደጋፍና ክትትል እውም ብለዋል ። በዘንድሮው አመት ለሚመጣው ምርጫ ሚድያው ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተከትሎ የሰው ሃይላቸውን ለማብቃት ሞያዊ ድጋፍ ለማድረግ ባለስልጣኑ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ።
ዘርፉ በተጠናቀቀው 2017 አመት በርካታ ተግዳሮቶችን ያስተናገደ እንደነበር ያነጋገርናቸው አካላት ገልጸዋል ። በቀጣይም በባለሙያው እንዲሁም በተቋማት ብሎም በመንግስት በኩል ዘርፉ ከተጋረጠበት ዘርፈ ብዙ ችግር ከመታደግ አንጻር በርካታ ሰራዎች እንደሚጠበቁ በዳሰሳው የተሳፈረ ሃሳብ ነው ።