የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እና የቱሪዝም ሚኒስቴር በቱሪዝም ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እና የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ናቸው።
ስምምነቱ የቱሪስቶችን ቆይታ ለማረዘም በሚያስችለው “ስቶፕ ኦቨር ቱሪዝም” ዘርፍ ሲሆን ተጓዦች ከመነሻ አገራቸው በሚነሱበት ጊዜ በመሸጋገሪያነት በኢትዮጵያ ሲያልፉ ጥቂት ቀናት በሀገሪቷ ቆይታ አድርገው ወደ መዳረሻ አገር እንዲሄዱ የሚያስችል የቱሪዝም ዓይነት ነው ተብሏል፡፡
ሶስቱ ተቋማት የተፈራሙት ስምምነት የአዲስ አበባ የቱሪዝም ዕድገትን ለማሳደግ ታሳቢ ያደረገና በከተማዋ የቆይታ ግዜ ለሚኖራቸው መንገደኞች በተዘጋጀ ስቶፕ ኦቨር ፓኬጅ ላይ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ምላሽ ይስጡ