ኢትዮጵያ በቀንድ ከብት ሀብቷ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከቀዳሚዎቹ 10 አገራት ተርታ የምትሰለፍ ሲሆን፣ በአፍሪካ ደግሞ ቀዳሚ መሆኗ ይገለጻል። ይሁን እንጂ አገሪቱ ይህን ያህል ግዙፍ ሀብት ቢኖራትም፣ ከዘርፉ የሚገኘው ገቢም ሆነ አርብቶ አደሩን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑ ይነገራል።
አርብቶ አደሩ ባለው የቀንድ ከብት ሀብት ልክ ተጠቃሚ እንዲሆን በርካታ ስራዎች ቢጀመሩም፤ አሁንም ድረስ በግንዛቤ እና በባህላዊ የአመራረት ዘይቤ ክፍተት ምክንያት፣ ንብረቱ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ሲጎዳ ይስተዋላል።
በዛሬው የዳሰሳ ጥንቅራችን፤ አርብቶ አደሮች ያላቸውን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ተጠቃሚ እንዲሆኑና ወደ ሌሎች የኢንቨስትመንት አማራጮች በመግባት፣ ከራሳቸው አልፈው ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ምን መደረግ ይገባል? የሚለውን ነጥብ እናስቃኛችኋለን።
አዘጋጅና አቅራቢ መዲና አውሰኢድ
ሙሉ ፕሮግራሙን ከተያያዘው ሊንክ ያዳምጡ
ምላሽ ይስጡ