ሕዳር 29 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እስራኤል እና የፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ሃማስ የረዥም ጊዜ የሰላም ዕቅድ ሁለተኛ ምዕራፍ ውስጥ “በጣም በቅርብ ጊዜ” እንደሚገቡ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት የጀርመን ቻንስለር ፍሬድሪክ ሜርዝን ካገኙ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
ኔታንያሁ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ከመሸጋገር በፊት ሃማስ ቀሪውን ታጋች አስከሬን መመለስ እንዳለበት እንደ ቅድመ ሁኔታ መዘርዘራቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ይህ ስምምነት የረጅም ጊዜ የጋዛን መረጋጋት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የመራው ባለ ሃያ ነጥብ የሰላም ዕቅድ ሁለተኛው ምዕራፍ እጅግ ውስብስብ የሆኑ ጉዳዮችን እንደሚያካትት ተገልጿል። ከእነዚህም መካከል የሃማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ መፍታትና ጋዛን ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ ማድረግ፣ የእስራኤል ወታደሮች ከጋዛ ግዛት ተጨማሪ መውጣት፣ በጋዛ የጸጥታን ለማስጠበቅ ዓለም አቀፍ የጸጥታ ኃይል ማሰማራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ቁጥጥር ስር ያለ ጊዜያዊ የፍልስጤም አስተዳደር መመስረት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የሰላም ዕቅድ ሦስተኛ ምዕራፍ እንዳለውም ጠቅሰው፣ ይህም ጋዛን ከጽንፈኝነት የማጽዳትና የረዥም ጊዜ መልሶ ግንባታን የማስጀመር ሥራን እንደሚያካትት ገልጸዋል። የሃማስ አመራሮች ግን የጦር መሣሪያዎቻቸውን ላለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን ፍንጭ ቢሰጡም፣ እስራኤል የሃማስን ሙሉ በሙሉ መደምሰስ የግድ እንደሆነ መግለጿ ስምምነቱን የበለጠ አወሳስቦታል።
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ 👉 https://t.me/menaharia_fm
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን 📞
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63 (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
ምላሽ ይስጡ