ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)ጀርመን በዓለም የመጀመሪያውን ሙሉ በሙሉ በሃይድሮጂን ኃይል የሚሰራ የባቡር መርከቦችን በማስጀመር በአረንጓዴ ትራንስፖርት አብዮት ግንባር ቀደም ሆናለች። እነዚህ የወደፊቱን የያዙ ባቡሮች ጸጥታ በሰፈነበት መንገድ የሚጓዙ ሲሆን፣ ምንም ዓይነት ካርቦን ወይም ጎጂ ልቀቶችን አያመነጩም፤ ከንጹህ ውኃ ትነት ውጭ። ይህም ወደ ንጹህ ኃይል የጉዞ ስርዓት ለመሸጋገር ታላቅ ምዕራፍ ነው ተብሎለታል፡፡
እስከ 140 ኪ.ሜ. በሰዓት ፍጥነት የመጓዝ አቅም ያላቸው እና በአንድ ታንክ ነዳጅ ብቻ እስከ 1,000 ኪ.ሜ. የሚደርስ ርቀት መሸፈን የሚችሉ እነዚህ ባቡሮች፣ እንደ ባቫርያን አልፕስ ባሉ አካባቢዎች በጸጥታ ይንቀሳቀሳሉ፤ ምንም ዓይነት ጭስ ወይም የካርቦን ዳይኦክሳይድ ልቀት የላቸውም ነው የተባለው፡፡
ይህ ደግሞ አውሮፓ በ2050 ዓ.ም. የካርቦን ገለልተኝነት ግቧ ላይ ለመድረስ ትልቅ እድገት መሆኑን ያመላክታል ተብሎለታል።
እነዚህ የሃይድሮጂን ባቡሮች የናፍታ ባቡሮችን በመተካት፣ በገጠር እና በከተማ መካከል በሚደረጉ ጉዞዎች ለዘላቂ ጉዞ አዲስ መስፈርት እያስቀመጡ ነው ተብሏል።
የሃይድሮጂን ባቡሮች በስፋት ጥቅም ላይ መዋል ከጀመሩ የካርቦን ልቀትን በእጅጉ መቀነስ፤የአየር ንብረት ጥራትን ማሻሻል፤በቅሪተ አካል ነዳጆች ላይ ጥገኝነትን መቀነስ፤አረንጓዴ ኢኮኖሚን ማፋጠን ላይ ጉልህ ሚና ሊኖራቸው ይችላል ነው የተባለው፡፡
የሃይድሮጂን ምርት ራሱ ከታዳሽ ኃይል (አረንጓዴ ሃይድሮጂን) የሚመጣ ቢሆንም ጀርመን የምታሳየው አይነት አመራር፣ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት በሚደረገው ትግል ውስጥ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ነው ተብሎላታል፡፡
__ #menahriafm
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm
ምላሽ ይስጡ