ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በክረምት ወቅት የተፈጥሮ አደጋዎች በስፋት ማጋጠማቸው የሚታወስ ነው፡፡
በተመሳሳይ በዘንድሮ አመት ለሚያጋጥም የተፈጥሮ አደጋ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ያስታወቀው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው፡፡
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም በኢትዮጵያ የደቡቡን ክፍል ጨምሮ በቋሚነት ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎች እንዳሉ ገልጸዋል።
ከዚህም ቀደም በሀገሪቱ የመሬት መንሸራተት፤ የጎርፍ አደጋ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ እና ሌሎችም የተፈጥሮ አደጋዎች ማጋጠማቸውን ጠቅሰዋል፡፡
አሁን ላይ ኮሚሽኑ ችግሮችን ቀድሞ መከላከል የሚቻልበት ስልትን የማዘጋጀት እና የነበሩ ስጋቶችን ለመቀነስም ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም የተከሰቱ አደጋዎችን እንደ መነሻ በመውሰድ ምላሽ መስጠት የሚቻልበትን፤ የግንዛቤ ፈጠራ እንዲሁም ሌሎች ዘላቂ ያላቸውን መፍትሔዎች እያከናወነ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በርካታ የተፈጥሮ አደጋዎች ተከስተው፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች መፈናቀላቸው፣ የንብረት ውድመት እና ሞት ማጋጠሙ የሚታወቅ ነው።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm
ምላሽ ይስጡ