ሰኔ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በህዝብ ተወካዮች ምር ቤት የከተማ መሰረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴና የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የዉጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣ ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ ውይይት ለማካሄድ ቀድሞ ጥሪ ያደረገ ቢሆንም የተገኝ ሰው ባለመኖሩ ከቋሚ ኮሚቴዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል፡፡
በህዝባዊ ውይይቱ የተገኘ ሰው ባይኖርም የሚመለከታቸው ባለድርሻ ተቋማት በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ከቋሚ ኮሚቴ አባላት በኩል ድጋሚ ህዝባዊ ውይይት ጥሪ ተደረጎ ምክር ቤቱ እስከመጨረሻው ሙከራዎችን በማድረግ ረቂቅ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት መፈተሸ እንደሚገባ አስትያየት የተሰጠ ሲሆን ፤ የከተማ መሰረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ በቀጠይ አዋጁ እስኪወጣ ድረስ ህጋዊ አካሄዶችን እንደሚከተል አረጋግጧል፡፡ የከተማ መሰረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባልና የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ከአዋጁ ተፋፃሚነትን በተመለከተ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ ሄለን ደበበ አሁን ላይ በመላው ሀገሪቷ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መሻሻሎች ያሉበት መሆኑን አበራርተዋል፡፡ ስራወ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ሊያጋጥሙ የሚችሉ ጉዳዮች በአዋጁ እንዳልተመላከተና በቀጠይ ከከተሞች ጋር የሚኖረውን ቅንጅታዊ አሰራሮች የቤት ስራ ተወስዶ እንደሚሰራበት ጠይቀዋል፡፡
የፍትህ ሚኒስትር ወ/ሮ ሃና አርዓያሥላሴ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ዜጎች በሌሎች ሀገራት ያገኙትን አይነት መብት በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የሌሎች ሀገራት ዜጎች እንዲያገኙ የሚያስችል የግንባታ ዘርፉን የሚያነቃቃ ተጨማሪ ኢንቪስትመንትን የሚስብና የስራ እድልን የሚፈጥር አዋጅ መሆኑን በማመላከት የትኛውም የሚወጡ ህጎች በጥንቃቄ ታይተው ህገ መንግስቱን ድንጋጌዎች የማይጥሱ መሆናቸው ተረጋግጠው እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡
በቀጣይ ህዝባዊ ወይይት ይኑር አይኑር የተባለ ነገር ባይሆንም ረቂቁ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 20 ቀናት ውስጥ ይፀድቃል ተብሎ እንደሚታሰብና ቀጠይ ሳምንት በሚደረጉ ውይይቶች ማስተካኪያዎች ታክሎበት ጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢዎች ተናግረዋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
ምላሽ ይስጡ