ሰኔ 12 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በባለስልጣኑ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ገልገሎ ኦልጂራ፤ እንደ አገር የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እና በአቀማመጥ ምክንያት የተበላሹ መድሃኒቶችን የማስወገድ ችግር መኖሩን ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጅ ከክልሎች አንጻር በመዲናዋ የተሻለ የማስወገጃ አማራጮች መኖራቸው ነው የተናገሩት።
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጥቶባቸው የሚገዙ እና በተቋማት የአቀማመጥ ጥንቃቄ ጉድለት የተነሳ ለብልሽት የሚዳረጉ መድሐኒቶች በርካታ መሆናቸውን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ በሌላ በኩል ጥቂት የመጠቀሚያ ጊዜ ያላቸው መድሃኒቶችም በብዛት ወደ ሃገር እንደሚገቡ አስታውቀዋል፡፡
በመሆኑ የአገልግሎት ዘመናቸው ያለፉ መድሃኒቶች በርካታ በመሆናቸው እንደሃገር ከፍተኛ ኪሳራን እያስከተለ እንደሚገኝ ነው ያስታወቁት፡፡
በባለስልጣኑ በኩል በተያዘው በጀት አመት ወደ 50 ሚሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ ያለው መድሃኒት መወገዱን አስረድተዋል።
ባለስልጣኑ በቁጥጥር ሒደት ፍሪጅ ውስጥ ቅቤን የመሳሰሉ ምግቦች ከመድሐኒት ጋር ቀላቅለው ያስቀመጡ እና እርምጃም የተወሰደባቸው እንዳሉ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
ምላሽ ይስጡ