👉ይህ አይነቱ አንቀጽ ዜጎችን ለሰብዓዊ መብት ጥስት የሚያጋልጥ ነው ሲሉ የምክር ቤት አባላት ተቃዉሟቸዉን ገልጸዋል፡፡
ሰኔ 10 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 37ኛ መደበኛ ስብሰባው በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበውን ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል፡፡
ከቀድሞ አዋጅ 780/2005 አንቀፅ 26 ንዑስ አንቀስ 3 ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀፅ 4 ቀርቦል፡፡ በዚህም በሽፋን ስር ወይም በግዴታ ስራ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከፍቃድ ውጪ ከግድያ ወንጀል ውጪ በሚፈፀም ወንጀል ተጠያቂ አይሆንም ሲሉ የተሸሻለው አዋጅ ያቀረቡት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሩ ተናግረዋል፡፡
ይህንንም በመከተል ለምክር ቤቱ ሃሳባቸውን ያቀረቡት የምክር ቤቱ አባላት ዜጎችን ለሰበዓዊ መብት ጥሰት የሚያጋልጥ እንደሆነና አንቀጹ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዉ ተቃዉመዉታል፡፡
ልዩ የምርመራ ዘዴን የሚያከናውን ግለሰብ የህዝብ ጥቅምን ለማስጠበቅ በመሆኑ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት የወንጀል ድርጊት ቢፈፅም እንኳን ከወንጀል ክስ ነፃ የሚሆንበትን አግባብ መደንገግ እንደሚያስፈልግ የተናገሩት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሩ ድርጊቱ ሊፈፀም የሚችለው ባለማወቅ ወይም በምርመራ ወቅት በሚፈጠሩ ነገሮች ሊሆን እንደሚችልም ገልፀዋል፡፡
ከምክር ቤቱ አባላት ታቁመሞን ያስከተለዉ አዋጅ የቀድሞ አዋጅ 780/2005 በመሻር አዋጅ ቁጥር 1387/2017 ተደርጎ በሶስት ተቃውሞ እና በአንድ ድምፀ ታቅቦ በአብላጫ ድምፅ ጸድቋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
ምላሽ ይስጡ