የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በቀጣይ አመት ለሚኖረው ሃገራዊ ምርጫ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሰራዎችን መስራቱን ገልጿል ። በተለይም ምርጫ በደረሰ ጊዜ የተጋነነ የአባላት ቁጥር የሚያቀርቡና አካታችነት የጎደላቸው አባላትን የሚያቀርቡ የተፎካካሪ ፓርቲዎች በርካቶች መሆናቸውን ገልጿል፡፡
ይህን ተከትሎ ለሚሰጠው የገንዘብ ድጎማ ሲሉ ፓርቲዎች የሚያቀርቡት የሴትና አካል ጉዳተኛ አባላትን ጉዳይ ቦርዱ ምን አይነት የቁጥጥር ስራዎችን ሊሰራ አቅዷል የሚለዉን መናኸሪያ ሬዲዮ ለዋና ሰብሳቢዋ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ፤ቦርዱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ፓርቲዎች በሚያቀርቡት የሴትና የአካል ጉዳተኛ አባላት ብዛት አካታችነትና ተመጣጣኝነት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑንና የአባላቱን ዝርዝር መረጃ ለመመዝገብ የሚያግዝና የበፊቱን ማንዋል አሰራር የሚያስቀር ዲጂታል አማራጭ መዘርጋቱን ገልጸው፤ ፓርቲዎቹ ምን ያህል አባላትን እንደያዙና የአካቶ መዋቅራቸውን ማየት እንደሚቻል ብሎም ይሄንን የሚቆጣጠር ግብረ-ሃይል መቋቋሙንም ተናግረዋል ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ቀጣዩን የሃገራዊ ምርጫ አካታችና ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ እንዲሆን እየሰራ መሆኑ በመግለጫው ተመላክቷል ።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
ምላሽ ይስጡ