የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ የሚደረገውን አስርና መንገላታትን እንደሚያቅና ይህንኑ ችግር ለመፍታት ጥረቶችን በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፅ/ቤታቸው እንደሚዘጉ ፤ አመራሮቻቸውና አባላቶቻቸው እንደሚታሰሩ እንደሚያዉቁ ገልፀው ቦርዱ የሚመለከታቸው አካላት አባላቶቻቸውን እንዲፈቱና ጽ/ቤቶቻቸውን እንዲከፍቱላቸውና የፖለቲካ ፓርቲዎች መብቶች እንዲከበሩ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ቦርዱ ይህንን እያደረገ አይደለም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ቢሮ ድረስ መጥቶ አቤቱታውን ማቅረብ ይችላልም ነው ያሉት፡፡
ቦርዱ በቀጣይነትም ችግሮች በዘላቂነት እስኪፈቱ ድረስ ድጋፍና ክትትሎችን ማድረግን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሰብሳቢዋ ሜላተወርቅ ኃይሉ አመላክተዋል፡፡
በስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ በፀጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ሳይደረግባቸው ቆይቶ በቅርቡ የማሙያ ምርጫ የተደረገባቸው አከባቢዎች ላይ በቀጣይ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡
__
ምላሽ ይስጡ