ዘመኑ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የባህል፣ ቅርስ እና ቋንቋን ለመመዝገብና ለመሰነድ ከፍተኛ እድል የሚሰጥ ነው ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሂሩት ካሳ ናቸው።
ቋንቋ ቅርስና ባህልን ከቴክኖሎጂ ጋር ማስተሳሰር ኢትዮጵያን ለዓለም ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል ይሰጣል ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘመናዊ የባህል ቅርስ እና ቋንቋ መልክዓ ምድር መፍጠር እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሁለተኛውን ከተማ አቀፍ የባህልና የቋንቋ ጉባኤን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ጋር በጋራ የፌደራል የመንግሥት ኃላፊዎችን ጨምሮ ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የተገኙ የስራ ኃላፊዎች እና ከየዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የባህል እና የቋንቋ ምሁራን በታደሙበት “ቋንቋ፣ባህልና ቴክኖሎጂ ለዕገት’በሚል መሪ ቃል ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡
ምላሽ ይስጡ